Ethiopian Genocide Prevention Movement in Europe.

የኢትዮጵያውያን የዘር ፍጅት መከላከል ንቅናቄ በአውሮፓ!

በሃገራችን የተከሰተውን ለውጥ ተከትሎ፣በተፈጠረው ክፍተት በመጠቀም፣ በአንዳንድ ጽንፈኛ ሃይሎች፣ እየተደጋገመ እየተፈጸመ ያለው፣ ማንነትን እና እምነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። በእነዚህ ማንነት እና እምነት ተኮር ጥቃቶች፣ዜጎች ከቤት ነበረታቸው ተፈናቅለዋል፣ የአካል እና የስነልቦና ጉዳት ሰለባ ከሆኑት በተጨማሪ፣ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ዜጎች፣ውድ ህይወታቸውን እንዲያጡ ተደረጓል።

ህግ በማስከበር፣ የዜጎችን በህይወት የመኖር እና የንብረት መብት የመጠበቅ፣ እንዲሁም የማስከበር ሃላፊነት ያለባቸው የመንግስት አካላት፣ ጥቃቶቹን በማስቆም ረገድ ያሳዩት ቸልተኝነት/ደካማ ተነሳሽነት፣ጽንፈኞቹን ለተደጋጋሚ የጅምላ ዘር ፍጅት ተግባራት እንዲቀጥሉ ምክኛት ሆኗል።

ይህን ሁኔታ በሚገባ በመረዳት እና ከመደራጀት በቀር ምርጫ አለመኖሩን በመገንዘብ፣በተለያዩ የአውሮፓ ሃገራት የምንገኝ በተለያዩ የሙያ ዘረፍ ላይ የምንሰራ ኢትዮጵያውያን፣በሃገር ቤት ፍትህ ላጡ ወገኖች፣ጉዳያቸው የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት አግኝቶ፣ጥቃት ፈጻሚዎቹ እና የማህበራዊ ሚድያውን ጨምሮ በተለያዩ መንገዶች፣የጅምላ ፍጅትን የሚያበረታቱ ግለሰቦችን፣ በፍትህ ተጠያቂ የማደረግ፣ የፍትህ ለግፍ ሰለባዎች የአውሮፓ ግብረሃይልን፣ መስርተናል።

ከዚህም አላማው በመነሳት፣በሃገራችን እየተፈጸመ ያለውን ማንነት እና እምነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት፣መረጃ የማሰባሰብ፣የጥቃት አደራሽ ጽንፈኞችን ማንነት በመለየት በህግ ተጠያቂ የሚሆኑበትን መንገድ መስራት፣በሰብአዊ ፍጥረት ላይ ጅምላ ፍጅት ያስተባበሩ፣የፈጽሙ፣ ፈጻሚዎቹን በመገናኛ ብዙሃን አማካይነት ያበረታቱ ቡድኖች እና ግለሰቦች ዓለም አቀፍ የዝውውር ማእቀብ እንዲጣልባቸው፣ንብረታችው እንዲታገድ፣ለማደረግ።የደረሰውን ጥቃት በአይነት እና በመጠን በመዘገብ፣ተጎጂ ወገኖች ካሳ የሚያገኙበትን ሁኔታ አስተባብሮ የመስራት ስራ ይሰራል።

የፍትህ ለግፍ ሰለባዎች የአውሮፓ ግብረሃይል ወደፊት በሁሉም የአውሮፓ ሃገራት ወኪሎች የሚኖሩት ሲሆን፣በቀጣይነትም ማንኛውም ያገባኛል የሚል ስብዓዊ ፍጥረት ከጎናችን በመቆም፥ በጊዜ፥ በክህሎትና በገንዘብ በመደገፍ ለአላማችን ከግብ መድረስ አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪ እናቀርባለን።

ከዚህም አላማው በመነሳት፣በሃገራችን እየተፈጸመ ያለውን ማንነት እና እምነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት፣መረጃ የማሰባሰብ፣የጥቃት አደራሽ ጽንፈኞችን ማንነት በመለየት በህግ ተጠያቂ የሚሆኑበትን መንገድ መስራት፣በሰብአዊ ፍጥረት ላይ ጅምላ ፍጅት ያስተባበሩ፣የፈጽሙ፣ ፈጻሚዎቹን በመገናኛ ብዙሃን አማካይነት ያበረታቱ ቡድኖች እና ግለሰቦች ዓለም አቀፍ የዝውውር ማእቀብ እንዲጣልባቸው፣ንብረታችው እንዲታገድ፣ለማደረግ።የደረሰውን ጥቃት በአይነት እና በመጠን በመዘገብ፣ተጎጂ ወገኖች ካሳ የሚያገኙበትን ሁኔታ አስተባብሮ የመስራት ስራ ይሰራል።

የፍትህ ለግፍ ሰለባዎች የአውሮፓ ግብረሃይል ወደፊት በሁሉም የአውሮፓ ሃገራት ወኪሎች የሚኖሩት ሲሆን፣በቀጣይነትም ማንኛውም ያገባኛል የሚል ስብዓዊ ፍጥረት ከጎናችን በመቆም፥ በጊዜ፥ በክህሎትና በገንዘብ በመደገፍ ለአላማችን ከግብ መድረስ አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪ እናቀርባለን።

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር !!

የፍትህ ለግፍ ሰለባዎች የአውሮፓ ግበረሃይልን አስመልክቶ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘትና የእንስቃሴው አባል መሆን የምትሹ በሚከተሉት አድራሻዎች ልትጽፉልን ትችላላችሁ፤

Telephone: +46704731818
+447970350860
E-mail: egpmeu@gmail.com

Following the changes that have taken place in our country, taking advantage of the gap created by some extremist forces, the recurring attacks based on identity and beliefs have reached alarming levels. As a result of these identity and religious attacks, citizens have been displaced from their homes, and in addition to victims of physical and psychological abuse, countless citizens have lost their precious lives.

The negligence of the government, which is responsible for enforcing the law, protecting the lives and property of citizens, and enforcing them, has led to the extremists continuing to carry out repeated massacres.

Recognizing this and recognizing that there is no choice but to organize, Ethiopians working in various European countries, at home, to the international community, the perpetrators and the social media, in various ways, promote mass murder, justice. We have set up a European Task Force to hold accountable victims of injustice.

With this in mind, there is a need for international sanctions against groups and individuals who have carried out mass killings of human beings, perpetrated, and encouraged the perpetrators through the media, identifying the perpetrators of the attacks based on their identities and beliefs. , To ensure that their property is frozen.

Victims of Injustice The European Task Force will be represented in all European countries in the future, and we call on all future human beings to stand by us, support us in time, skill and money to contribute to the achievement of our goals.

 

About expeder

Check Also

ከኢትዮጵያዉያን ማህበር በአዉሮፓ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

PressRelease-AMHARIC- by A.E.E-March 23-2024

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

+ 73 = 75